Posts

Showing posts from 2018

አገር ቤት ደርሶ መልስ....

ባህርዳር...  እንደ ደረስን ወደ ሆቴላችን በባጃጅ ለመሄድ ሃሳቡ ነበረን።  ሻንጣችንን ከመኪናው ላይ ያወረደው ልጅ ግን፤ ..."ጋሼ እኛ ባጃጅ የሌለን ምን ስርተን እንብላ? ሆቴላችሁ እዚህ ቅርብ ነው። ኑ ተከተሉኝ"!.... እንዳለውም አምስት ደቂቃም ሳንራመድ ደረስን። እውነቱን ነው።  አሳዘነኝ። አንድ ወዳጄ እንዳጋጣሚ ለስራ ጉዳይ እዚያው ባህርዳህ መጥቶ ሆቴል ይዞ ስለነበር... ጣና ባህሩ ዳር ወስዶ ጥሩ ራት ጋበዘን። ይሁን እንጂ ልጄ አይነቱ በዛበት መሰለኝ... አሞት አደረና በሚቀጥለው ቀን ያቀድነው ፕሮግራም ሊካሄድ አልቻለም።  እኔም መጽሃፍ እያነበብኩ ከሆቴሉ ሳልወጣ ዋልኩ። አንድ ዘመድም ስለነበረኝ ረፋዱ ላይ የርሱን ልጆች ላይ ሄድኩኝ። በማግስቱም ጥዋት የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የባህርዳር ጽ/ቤት ካረፍኩበት ሆቴል ቅርብ ስለነበር ሰተት ብዬ ሄጄ ተዋወኩዋቸው። የፖለቲካ ፕሮግራማቸው ገና አልቆ ስላልተበተነ ላገኘው ባልችልም፤ በመሬት የግል ይዞታና በኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄ ላይ ጥሩ የሃሳብ መለዋወጥ አድረግን። ስለ አብንና አዴፓ ግንኙነት በሚመለከት ከነርሱ የተሰጠኝ መልስ ግን ስጋት ውስጥ ጣለኝ። አዴፓ አብንን ለማጥፋት እንደሚሰራና አብን በህዝቡ ድጋፍ ብቻ ህልውናው ሊጠበቅ እንደቻለ አስረዱኝ። አዴፓ ያሰረባቸውን አባሎቻቸውንም ህዝቡ እንዳሰፈታቸው ነገሩኝ። ይኼንኑ ስጋቴን  አዲስ አበባ ተመልሼ እኔ አባል ለሆንኩበት የአማራ ህልውና የኢትዮጵይ አንድነት ድርጅት ሰዎች ነገርኩዋቸው።   የአማራ ህልውና ለኢትዮጵይ አንድነት አመራሮች ከሁለቱንም ከፍተኛ የፖለቲካ ድርጅቶች አመራሮች ጋር ተነጋግረዋል። ድርጅቶች እየተቀራረቡ ሲመጡ ሊፈታ የማይችል ምንም አይነት ጉዳይ እንደማይኖር ነው የሚያስቡትና እን...

አገር ቤት ደርሶ መልስ...

አገር ቤት ደርሶ መልስ... ከስምንት አመታት በሁዋላ ኢትዮጵያ ደርሼ ተመለስኩ ። ብቻዬን አልሄድኩም። ጎረምሳውም ዘንደሮስ ተለይቼህ አልቀርም ስላለ ሁለት ራሴን ሆኜ ነው የሄድኩት። በቶሮንቶ አለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ዴሪም ላይነር ለመሳፈር... በተሽከርካሪ ወንበር ላይ የተቀመጡ ስድስት አሮጊቶች ተገፍተው ቀደም ብለው ገቡ። አንድም በሚገፋ ተሽከርካሪ ወንበር ላይ የተቀመጡ ሽማግሌ ባለማየቴ ይመስለኛል ...አንድ ትዝብት ትዝ ብሎኝ ብቻዬን ፈገግ አልኩ። እንዲህ ነው ነገሩ። ..."አባቶቻችንና እናቶቻችን ይጨቃጨቃሉ። በተለይ ውሃ ቀጠነ ብለው ነገር የሚያነሱት ብዙውን ጊዜ አባቶቻችን ናቸው። ታዲያ እግዚአብሄርም ይኼን አየና... እነሱን ቀድሞ በመውሰድ እናቶቻችን ቀሪውን እድሜያቸውን እፎይ ብለው እንዲያሳልፉ ያደርጋል ይባላል።" እነሆ በድሪም ላይነር የሰሜን አሜሪካ ክረምት ሲገባ ወደ ኢትዮጵያ...ሲወጣ ደግሞ ወደ አሜሪካ እየበረሩ እፎይ ማለት ነዋ! እናቶች ይመቻችሁ! አባቶችም አደብ ግዙ! በአሊታሊያ፣ በአሜሪካ፣በካናዳ፣በኬኤሌም፣ በሉፍንታዛና በብሬትሺ ኤር ወይስ በተደጋጋሚ በርሬያለሁ። በእነዚህ አየር መንገዶች ውስጥ አንድ የጎላ ፊት ይታያል። አብዛኛው ተሳፋሪ ፈረንጅ ነው። አልጠላውም። ግን ብቸኝነት ይሰማኛል። በኢትዮጵይ አየር መንገድ ስበር ሁለተኛዬ ነው። የተሳፋሪው ፊት.... አፍሪካውያን፣እስያውያና ፈረንጆችንም ስለሚያካትት  አለም አቀፋዊ ነው። በዚህም መሰረት በበረራ ወቅት የባይተዋርነት ስሜት በጭራሽ አይኖርም። በመቀጠልም የደስ ደስና ትህትና ያላቸው እህቶቻችን ለአዋቂ ይሁን ለልጆች ተሳፋሪዎች የሚያሳዩት እንክብካቤ የሚደነቅ ነው። ምንም የመሰልቸት ፊት አያሳዩም። በተጠሩ ቁጥር ከነፈገግታቸው ከች ነ...

መልሰ ብዬ ሳየው...4

... አሳዬ ከሐሰን ቱሬና ከከዲር ዋቆ ጋር ተገኛኝተው መንግስት ደኑን በጄት ለመደብደብ አስቧልና ይህ ጉዳት ከመደረሱ በፊት በሰላም እጃቸውን ለመሰጠትና የሚይቀርቡትም ቅደመ ሁኔታ ካላ ቀጥታ ከእንደራሴው ጃጋማ ኬሎ ጋር ለሁለቱም አመቺ ቦታ ፈልገው ለማገናኘት እንደሚሞክሩ   ባቀረቡት ሃሳብ መሰረት ... ሐስንም ሆነ ከዲር እንዲሁም ሁሴን ዳዲ፤ በከር ጂሎና ሐጂ ተመካክረው ተስማሙ። መጀምሪያ ግን  ከከዲር ዋቆ ወደ ሰላም እንዲገባ  እንፈልጋለን። እኛም ሁኔታውን እያየን ተራ በተራ ወደ ሰላማዊ ኑሮአቸው ለመመለስ ማለትም እጅ ለመስጠት ፍላጎት አለን።   ካሳሁን ስምምነቱን ይዘው ከሃሰን ቱሬ ሰላይ ኡመር ሃስን ጋር ወደ ጎባ በማቅናት ከእርሳቸውም ሆነ ከሐሰን ቱሬ ወዳጅ ከሆኑት አቶ ንጉሴ ገረመድሕን ቤት በሁለተኛው ቅዳሜ እቴቱ ላይ ደርሰው አዳር ያደርጋሉ። እቴቱ ከጎባ 10 ኪሎ ሜትር የምትርቅ የገጠር ቀበሌ ናት። በማግስቱም ኡመርን ንጉሴ ቤት ትተው እነ ከተማ ከእንቅልፋቸው ገና ሳይነሱ፤   ልጆች! ከተማ! አቡ! በሩን ክፍተሉኝ ሲሉ ተጣሩ። አሳዬ ጃጋማን በአስቸኳይ ለማነጋገር ቀርቶ ስልጣናቸውም በቀጠሮ እንኳን ቢሆን ለማነጋገር ስለማያስችሏቸው ዘዴ መፈለግ ነበረባቸው። ጊንር ሰራተኛ በነበሩበት ጊዜ በጣም ወዳጃቸው ና ጃጋማን በቀላሉ ለማግኘት የሚችል በቀለ ቱሉን ማነጋገር ነበረባቸው። እንዳሰቡትም በቀለ በሌላ ሁነኛ ሰው በኩል መልእክቱን ለጃጋማ እንዲድደርስ አንደረጉ። ጃጋማም በመገረም አቶ ከበደን ሰኞ ጥዋት በ 2.00 ቢሮአቸው እንዲመጡ አስጠሩዋቸው። ማ ታውኑ ከበደ የሆነውን ለካሳሁን ሲነግራቸው በጣም ተደስተው ጃጋማ ከተመቻቸው ንፍስ ለመቀበል ብለው በመኪና እቴቱ ድረስ ላይን ያዝ ሲል ቢመጡ ኡመርን...

መለስ ብዬ ሳየው 3

አቶ አድነው ስለ ኸረና ዘመቻ የሚያወጉት ሞልቶአቸዋል። “ሽፍቶች ሸሽተው ወደ ኸረና ደን ውስጥ ስለገቡ የረባ ጦርነት አልገጠመንም። ይሁን እንጂ፤ ነጭ ለባሽ መዝናናት አብዝቶ ነበር። አንድ ቀን ፍታውራሪን አጅበን ለአሰሳ ፈት ፊት ሲሄድ ዛፍ ሲወዛወዝ አየሁ። ዝንጀሮ ነው! ጉሬዛ ነው! ቢሉኝም አላመንኩም። ፍታውራሪም ተው ዝንጀሮ ነው አሉኝ። የለም እምቢ ብዬ ተኩስ ከፈትኩ!” “ወዲያው ከሽፍቶች አንዴ እሩምታ! ታ!ታ! ድም! ድም! ድብልቅልቅ ያለ ውግያ ሆነ። አድፍጠው ሊጨርሱን ነበር!ተከታተልናቸው!የታባታቸው! አመለጡን”!   ፍታውራሪም በዚህ ተደስተው ነፍሴን ያተርፍካት አንተ ነህ እያሉ ስለሚያሞግሳቸው አቶ አድነው በንቁነታቸው ይኩራራሉ። አድነው የማር ነጋዴነታቸውን ትተው በሀረና ዘመቻ ባሳዩት ወታደራዊ ንቃት የወህኒ ቤት ዘበኛነት ተቀጥረው ደሞዝተኛ ሆኑ። የንጉሱ ጉብኝትና የሰላም ጥሪ ዋናው ሽፍታ ዋቆ ጉቱ እጃቸውን ቢሰጡምና የባሌም ሽፍትነት በመንግስት ጦር ቢፈታም፤ ኸረና የመሽጉት የዋጎ ጉቱ ቀኝ እጆች፤እነ ሐሰን ቱሬና ከዲር ዋቆና ሁሴን ዳዲና የመሣሰሉት አሁንም እጅ አልሰጡም። ኸረና ከጎባ በስተደቡብ የሚገኝ ጥቅጥቅ ያለ ደን ነው። በመሆኑም እዚያ ውስጥ ወታደርም ሆነ ነጭ ለባሽ መላክ ሰው ማስጨረስ ካልሆነ ትርፍ ስለሌለው የቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ አገዛዝ ችግሩን በሰላም ለመፍታት ወይም አካባቢውን በአውሮፕላን ለመደብደብ ወስኗል። ገብሬ ሞረዱ ጡ!ጡጡ!ጡጡጡ!ጡጡ!ጡጡጡ “ንጉስ ነገስትህ!ንጉስ ነገስትህ! ኃይለ ስላሴ!ኃይለ ስላሴ! ሊ ጎ በ ኙ ህ! ሊ ጎ በ ኙ ህ! ይመጣሉና!ይመጣሉና! ጡ!ጡጡ!ጡጡጡ!ጡጡ! ቀዬህን አፅዳ! አጥርህን እጠር!   በርህንም ቀለም ቀባ! ብለውሃል! ጡ...

መለስ ብዬ ሳየው…2

መለስ ብዬ ሳየው….. ከቦጋለ   ካሣዬ ነጭ ለባሽ ሽፍታን ለመውጋት ዘምቷል። አዝማቹ ጣሊያንን በአርበኝነት ያርበደበዱት ጀግናው ፍታውራሪ ተገኔ ተሰማ ናቸው። ወንድማቸው ካፒቴን አጥሬ ተሰማ፤ ኢጣሊያ ተሸንፎ በማፈግፈግ ላይ እያለ አሳደው ከሰብስቤ ዋሻ ላይ በመማረክ እንደከብት አርደው ደሙን መጠጣታቸውን ድፍን ባሌ ያውቃል። የነ ከተማም አህያና ቆፍጣናው አጎቱ ዘምተዋል። የአጎቱ ሚስት ዘነበች ጉርሙ መሬት ይቅለላትና በሳንባ ነቀርሳ በልጅነቱ የተቀጨውን ብዙየን፤ ባሉዋ በዘመተ በሶስተኛው ቀን ወልዳ አራስ ናት።   ለአራስ ጠያቂ ተገንፍቶ የሚተረርፈውን ገንፎ ከተማና የአጎቱ ልጅ ጉቱ እየበሉ፤   አፋችሁን ተግሞጥመጡ! ምች እንዳይመታችሁ! የሚሉት ማስጥንቀቂያዎችም ሆነ ገንፎው ራሱ አንገሽግሾአቸዋል። የልጅ ነገር ሆዴን አመመኝ እንጂ መቼ በቃኝ ያቃል? ከበሉ በሁውላ ሮጠው ለመጫወት የሚሄዱት የሰፈሩ ልጅ ሁሉ የሚሰበሰብባት ሆን ተብሎ ለእግር ካስ ሜዳ የተሰራች የምትመስለው ሜዳ ላይ ነው። የከተማና የጉቱ አያት ሜዳዋ ሳር ስለምታበቅል ሳሩን አጭደው ከከመሩ በኋላ ዝናብ እስኪዘንብ ድርስ የሰፈሩ ልጆች ሜዳዋ ላይ ኳስ ቢጫወቱባትም ሆነ የሩጫ   ወድድር ቢያደርጉባት አይቆጡም። ሌላ ጊዜ ግን ውርድ ከራሴ ነው! ድርሽ ማለት የለም። የተያዘ በሳማ ነው የሚለበለበው። ነጭ ለባሽ ውጊያውን እያፋፈመው ነው። የእሳቱ ነበልባል ፋሲል ተራራን ከሩቁ ወለል አድርጎ ያሳያል። ከሜዳዋ ላይ የቃጠሎውን ትእይንት ለማየት የሰፈሩ ልጆች ተሰብሰበው፤ ኸረ ጎበዝ! እህም ነው!! ሽፍታ ጠግቧል እህም ነው!! እንበለው!! ልጆች እንደዛ ሲፈነጥዙ እናቶቻችው፤"ኸረ እናንተ ልጆች ወደ ቤት ግቡ!" "ወየውላቸው ዛሬ!" በማለት...

መለስ ብዬ ሳየው... (ቦጋለ ካሣዬ)

..."ጥሩ ገንዘብ እዛ የተማሪ እግር ኩዋስ ሜዳ ውስጥ ገብታለች! ሂድና ቶሎ ይዘሃት ና!" ወረፍ ሳይበዛ እንሄድ!" የአቡ እናት የተለመደ ትእዛዝ ነው። የጥሩ ገንዝብ እናት ከአህይት ሌላ የተለየ ስም ሳይወጣላት ጅብ በላት። ጥሩ ገንዘብ... ገና አሃዱ ተብሎ ከጀርባዋ ላይ ጭነት ያረፋባት ቀን እንደሌሎች ልትለግም ይቅርና ... አልፋ ተርፋ... የአህዮች ፊት መሪ በመሆኑዋ ነው ጥሩ ገንዝብን የመሰለ ስም ከአቶ አሳዬ የተቻረቺው። ወረፋው ደግሞ የወፍጮ ቤቱ ነው። ጋሽ መሃመዶ ይባል ነበር ተቆጣጣሪው። በጣም ደግ ሰው ነበር። መቼም በህይወት ሊኖር አይችልም.... እድሜ እንደ ማቱ ሳላ ተለግሶት ካልሆነ። .."አንተ አቡ ቆይ! ቆይ! የጋሼ አሳዬ ልጅ አይደለህ? አዎ! አህያዋን(ጥሩ ገንዘብን) ነጭ ለባሾች ስንቃቸውን ጭነውባት ሄደዋል በለው! አይዚህ አይቆጣኽም! ነጭ ለባሽ የአገር ፀጥታ ሲደፈረስ ከመደበኛ ሰራዊት ውጭ ሰላም እንዲይስከብር የሚጠራ ዘማች ነው። ነፍጠኛ የሚሉት ነው። አማሮች ብቻ አይደሉም ታዲያ። ሰላሌዎችና ጉራጌዎች አሉበት። ባሌ ጎባ ድሮ ጠሃይ ከጠለቀ በሁውላ ድቅድቅ ባለ ጨለማ ነው የምትዋጠው። ሰማዩ ካልዳመነ ግን ከዋክቦቶችዋ የሚሰጡት ብርሃንና በተለይ ተወራርዋሪዎቹ የሚሰሩት ትእይንት ታይቶ የሚጠገብ አይደለም። ወቼ ጉድ ...አንድ አውራጃ ሙሉ አገር ከዋክብት ለማየት እንድንችል የመንገድ ዳር መብራት እንዳይተከልበት! ብለው አሻፈረኝ ያሉት የፍሪዢያን ፈርንጆች... ደሜን ከደማቸው በመቀላቀሌ ይሆን? ስለ ከዋክብት ሳነሳ ትዝ አሉኝ። ከዋክብትን ማየት ማራኪ ነው። ጎባ የእዛን እለት ግን ዝናብና ደመና ነው። ይህም ሆኖ ድሮ ከጎባ በስተደቡቡ በጭራሽ በጨለማ የማይታየው የፋሲል ተራራ በአካ...

አብይ አህመድ፤ ትን! ብሎት ግጥም ቢልስ?

ሳር ቅጠሉ፤ አብይ! አብይ! ሆኖአል፡፡ አማን! አማን አንዶም! ፤ መንጌ መንጌ! የተባሉበትም ጊዚያት ነበሩ፡፡ መለስ ዜናዊ መሌ ተብሎ አያቅም፡፡ ራሱም ባንዳና አያቱም ባንዳ ስለነበሩ እኛም እንደጠላነው እርሱም እንደጠላን አምላክ ጠራልን፡፡ አዎ...ድፍን ትግሬ ይወደው ነበር። ከዚያም ዱቤ መጣ፡፡ ዱቤ ማለቴ እርሱም ሆነ ሌላ ማንም ሳያስበው ጠቅላይ ሚኒስተር የመሆኑን ድንገተኛነት ለመጠቆም ነው፡፡ ሃይለማርያም በትምህርቱም ሆነ በተመክሮው ከማንም ባያንስም ጥርስ የሌለው አለቃ ሆኖ ወንጀልም ፈጥሞ ተሰናበተ፡፡ አማንን መንግስቱ በላው፡፡ መንግስቱም 17 የስልጣን አመቱን ሰው ሲገድልና በመፈክር ኢምፔሪያሊዝምን ሲደመሥስ፤ ስልጣን ህዝባዊ ይሆን ዘንድ ምንም ስራ ሳይሰራበት አለቀና ለስደት ተዳረገ፡፡ ለነገሩ  ነው እንጂ ከመንግስቱ መቼም ዴሞክራሲ ይጠበቃል ብዮ አይደለም፡፡፡ ወያኔ ስልጣን በያዘ ማግስት የመንግስቱን ሰለባዎች እየሰበሰበ ማስለቀስ ጀምሮ ነበር፡፡ አንድ በጣም በሳል እመቤት ይኽንኑ ታዝባ፤ ለሃይሌ ገሪማ የሰጠቺው አስተያየት እስከዛሬ አይረሳኝም፡፡ ብዙም ሰው ግን የረሳው ይመስላል፡፡ እመቤቲቱ ምን አለች? ቃል በቃል ባይሆንም መልእክቱዋ....የእኛ ነጻ መሆን እኮ የሚለካው ደርግ በመውደቁ አይደለም። የሚለካው ሕዝቡ እውነተኛ የስልጣን ምንጭ ሲሆን ብቻ ነው ነበር ያለቺው። አረገቴ? አብይ! አብይ! አብዬዎች? የፖለቲካ ባህላቸው ያልበሰለ ሰዎች ስሜት ይገዛቸዋል፡፡ ደግ ነው ብለው የሚይስቡት መሪ ላይ እምነታቸውን ይጥላሉ፡፡ አንድ ግለሰብ መሪ ግን እንደ ሸክላ ተሰባሪ መሆኑን ላንዳፍታም ያጤኑት አይስመስልም። እስኪ ዛሬ አብይ ትን ብሎት ቢያልፍ ነገ አገሪቱ ምን ትሆናለች? ሌላ አብይ እንደሆነ አይመጣም፡፡ ኢትዮጵያ እስካሁን ወደሁዋላ የቀረ...