Posts

Showing posts from 2025

መሬት ላራሹ!

Image
  አንድ ለመንገድ.... ወ/ሮ ታደለች ኃይለሚካኤል፤ በ“ዳኛው ማነው ?” [1] መድብላቸው የመሬት ላራሹ መፈክር ለኩዋሸ፤ የትግራይና የወሎን ገበሬዎች ችጋር በለጋ እድሜው ያስተዋለውና የኪነ-ጥበብም ፍቅር የነበረው ባለቤታቸው ብርሃነ መስቀል ረዳ እንደሆነ ነግረውናል። የመሬት ስሪት እንዲሻሻል በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጊዜ የነበረው የህግ መወሰኛ ምክርቤት፤ ለአንድ ሰው በይዞታ እስከ 90 ጋሻ መሬት(90*40 =3600 ሄክታር) መብለጥ የለበትም የሚለውን ጣራ መቃወሙንም ይጠቅሳሉ። ማነሱ እኮ ነው ጃል! አስገራሚ ተቃውሞ ነው። ደራሲዋ የመሬት ላራሹ፣የብሄረሰብና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች የተሳሰሩ ናቸው ይሉናል። የሆኖ ሆኖ እስከ ዛሬ በደርግ የታወጀው አዋጅ አራሹን በዘላቂነት የመሬት ባለቤት እንዳላደረገው፤ የወያኔ/ኢሕዴግ ይሁን የቀጠለው የብልጽግና/ኦሆዴድ ስርአቶች መሬት የብሄረተኛ ኢሊቶች መበልጸጊያ እንዲሆን በማድረጋቸው የባለቤታቸው መሬት ላራሹ መፈክር በተግባር እንዳልዋለ ያስረዳሉ። የግል መሬት እንደማንኛውም ቁዋሚ ንብረት የግል ካልሆነ፤ አራሹ ላቡንም ይሁን ጥሪቱን በመሬቱ ላይ አፍሶስ ምርታማነቱን ለማሳደግ ልቡ መንታ ነው የሚሆንበት። ነገ እፈናቀላለሁ ብሎ ይሰጋል፡፡  የመሬት ምርታማነት መጨመር በቀጥታ ከግል ይዞታ ጋር የተያይዘ ነው የሚሉ ጥናቶች አሉ። የብዙ የአፍሪካ አገሮች የመሬት ስሪት በመንግስት ቁጥጥር ሥር ነው።  መሬት በግል ይዞታ እንዲያዝ የፈቀዱት ምስርና  ሞሮኮ የመሬታቸው ምርታማነት በመንግስት ይዞታ ስር ከተያዙት አገራት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ነው። በመሬት ይዞታ ላይ ጥናት በማድረግ የሚታወቀው  ደሳለኝ ራኽመቶ፤ የኢትዮጵያ ገዢዎች መሬት የግል ከሆነ ገበሬው ሽጦት ከተማ በመግባት ስራፈት ...

ትንሹ እስክንድር ነጋ!

Image
                         ትንሹ እስክንድር ነጋ፤ ጋዜጠኛና አርበኛ ጌጥዬ  ያለው ባለፈው ስለ አንዳንድ አሞላቃቂ ጥቅመኞች የኢሳት ፍርስራሽ ሚዲያዎች የከሰረ የጋዜጠኝነት ስነምግባር ይዘቶች በደምሳሳው አይተናል። ዛሬ አንድ ሌላ ማንሳት በሚገባን፤የኢትዮ-360ው፤ አይጠገቤ ጋዜጠኛና አርበኛ ጌጥዬ ያለው እንጀምር። ጌጥዬ በሞራል ከፍታው ትንሹ እስክንድር ነጋ ሊባል የሚገባው ነው።ከትግል ሜዳ ሆኖ ከየፋኖ ውሎ ፕሮግራሙ በተጨማሪ፤ የሚሰጣቸው ትንታኔዎች ሰፊና ጥልቅ ንባቡን የሚያንፀባርቁ ናቸው። የማያውቀውንም አላውቅም ነው የሚለው። ትሁትና የሰላ አእምሮ ነው ያለው። ሲወድም ሲተችም አያዳላም። እውነተኛ ሰው ነው። የጌጥዬ የድምፅ ፍሰትና ቃና አድማጭን ከመቀመጫው እንዳይነቃነቅ የሚያደርጉ ማግኔቶች ናቸው።ሌሎች ከጊጥዬ መማር አለባቸው።በሚዲያ ላይ ቀርቦ መቆጣትና መደንፋት የአድማጭን የማድመጥ አትኮሮት ይቀንሳሉና።በዚህም መሰረት ኢትዮ-360 ለእውነት በቆሙ የአማራ ይሁን የኢትዮጵያ ልጆች የተካተቱበት ስለሆነ በገንዘብም በሃስብም ሊደገፍ የሚገባው ተቁዋም ነው። ከኢሳት ፍርስራሾች ውጭ ብዙ ሚድያዎች አሉ።የጣና ቲቪ እስካሁን ለፋኖ ትግል እየሰጠ ያለው አበርክቶ ግሩም ነው። ከኢትዮ-360 ጋር ስራቸውን በቅንጅት ሊሰሩ ቢችሉ ጥሩ ይመስለኛል፤ ችግር ከሌለ።አብረው ለፍኖ መሪዎች ጥሪ በማድረግ የአመራር ብቃታቸውን ህዝብ የሚመዝንበትን መድረክ ማመቻቸት ይችላሉ። ጥሪ አድርገው እምቢ የሚሉትን ለህዝብ ማሳወቅ ይገባቸዋል። ይኼን ማድረግ ጥቅሙ ብዙ ነው። እንደው በጥቂቱ፤ መጀመሪያ የፋኖ ግለሰብ ታጋይ እውነተኛ መሪዎቹን በትክክል እንዲያውቅ ያ...

አሞላቃቂ ጥቅመኛ!

ስልጡን ይሁን ገልቱ አመራር በስልጣን ላይ የማስቀመጥ ሃላፊነት የሕዝብ ነው፡፡ሕዝብ ደግሞ ሃላፊነቱን በቅጡ ለመወጣት እውነተኛ መረጃ ያስፈልገዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ካለመታከት መልካም ስነምግባርን በማበረታታት፤ ለሕብረተሰብ የማይጠቅምን ድርጊት ይሁን ሃሳብ ጠንቅነቱን በማስተማር፤ ለህዝብ ቆመናል በማለት የሚሞላቀቁትንና ሃቀኞቹን የስልጣን ተፎካካሪዎች ተከታትለው ማንነታቸውን በማስተዋወቅ  ትልቅ አጋዥ ሚና ሊጫወቱ ይገባል፡፡ ፋኖና የኢትዮጵያ ዲያስጶራ ሚዲያዎች ፋኖ ባለፉት 2 አመታት የትጥቅ ትግል ከጀመረበት ጀምሮ በማህበራዊና በሳተላይት መረጃ የሚያስተላልፉትን ሚዲያዎች፤ የኢሳት ፍርስራሾችና ሌሎች ብለን ልንከፍላቸው እንችላለን፡፡ የኢሳት ፍርስራሾች ወያኔን ለመታገል በግንቦት 7 የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን(ኢሳት) የዲያስጶራው ድጋፍ ነበረው፡፡ብዙዎቹ ጋዜጠኞቹም ወያኔ በቅንጅት መሸነፉን አልቀበልም ብሎ ባሳረፈባቸው ዱላ አገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ናቸው። ኢሳት ወያኔን ታግሎአል። ይሁን እንጂ በግንቦት 7 ፖለቲከኞች ቁጥጥር ስር ስለነበረ ነጻ ሚድያ አልነበረም። ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ከሻእቢያ ጋር መስራት እንደጀመሩ፤ኢሳት ለብሄረተኞች ሰፊ መድረክ በመስጠት በቅንጅት መንፈስ ጠውልጎ የነበረውን ጎሰኝነት እንዲለመልም አፍራሽ ሚና ተጫወተ። የግንቦት-7ን የፈጠራ ወታደራዊ ኮሚንኬ በማስራጨት አማራው በተለይ በጎንደር በወያኔ እንዲመታ ዱላ አቀበለ። ኢሳት ሁነኛ ተቁዋም ሆኖ እንዲዘልቅ ከግንቦት 7 ይላቀቅ የሚለው ውትወታ በጊዜው ስሚም አላገኘም፡፡ የአገር ፍቅር እንጂ የፖለቲካ እውቀት የለኝም የሚለው የኢሳት የገንዘብ ዋና አሰባሳቢ አርቲስት ታማኝ በየነ፤ “ኢሳት የግንቦት 7 ቢሆንስ?” እያለ ይሳለቅ ነበር።...

የፋኖ አንድነት እንዴት?

ቦጋለ ካሣዬ/2025 የዚህ መጣጥፍ ዋና አላማ የፋኖ አንድነት ሕዝባዊነቱን ጠብቆ እንዲረጋገጥ ቅንና ግልጽ ውይይት መቆስቆስ ነው።በጎደለ መረጃ ሊዳብር ይገባል። መነሻችን/መድረሻችን እንደሚታወቀው የአማራ ፋኖ፤ለምሳሌ በትግሉ መነሻና መዳረሻ ጉንጭ አልፋ ሰበቦች ወደ አንድ የፋኖ አደረጃጀት ሊመጣ አልቻለም። መነሻችንም አማራ መዳረሻችንም አማራ የሚሉት፤ አብይን ከስልጣን አውርደን ብቻችንን ወይም ሊፎካከሩን ከሚችሉ ነገዶች ጋር ስልጣን ተጋርተን፤ የወያኔን ህገ መንግስት ትንሽ አሻሽለንም ይሁን እንዳለ ተቀብለን ኢትዮጵያን እናስተዳድራለን ማለት ነው። መነሻችን አማራ መዳረሻችን ኢትዮጵያ ደግሞ ወያኔ የተከተለውን የጎሳ ስርአት ነቅለን በኢትዮጵያዊ ዜግነት ላይ የተመሰረተ አዲስ ስርአት ተክለን ኢትዮጵያን እንታደጋለን ነው። እንደ የሸዋ ፋኖ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ዶ/ር አብደላ እድሪስ ከሆነ ግን፤በዘመነ ካሴ የሚመራው የጎጃም አማራ ፋኖ ፣በሻለቃ ምሬ ወዳጆ የሚመራው የወሎ ፋኖና በሻለቃ ባዬና በሻለቃ ሃብቴ የሚመራው የጎንደር አንድነት የወያኔው መለስ ዜናዊ ፈለግ ተከትለው፤ መነሻችንም አማራ/መዳረሻችን አማራ ነው መንገዳቸው።ጄኔራል ተፈራ ፋኖን ከተቀላቀለ በሁዋላ ከሜዳ የሰጠው አስተያየት የአስራትን ፈለግ የተከተለ ቢሆንም እርሱ የተቀላቀለው የሸዋ ፋኖ አቁዋም ግን የወያኔን ህገመንግስት አጥብቆ የሚደግፍ ነው። ጀኔራሉ ከልብ የአስራትን ፈለግ ተከታይ ከሆነ ለምን ወደ መከታው አልሄደም? በፋኖ እስክንድር ነጋ የሚመራው የአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት(አፋሕድ) ስር የተደራጁት እዞች ደግሞ፤ መነሻችን አማራ መዳረሻችን ኢትዮጵያን ነው የሚያራምዱት።የልዩነታቸውን ሰበብ እስኪ በወፍበረር ከአደረጃጀታቸው ተነስተን እንቃኝ። የፋኖ አደረጃጀት የወያኔን...