Posts

Showing posts from August, 2018

መልሰ ብዬ ሳየው...4

... አሳዬ ከሐሰን ቱሬና ከከዲር ዋቆ ጋር ተገኛኝተው መንግስት ደኑን በጄት ለመደብደብ አስቧልና ይህ ጉዳት ከመደረሱ በፊት በሰላም እጃቸውን ለመሰጠትና የሚይቀርቡትም ቅደመ ሁኔታ ካላ ቀጥታ ከእንደራሴው ጃጋማ ኬሎ ጋር ለሁለቱም አመቺ ቦታ ፈልገው ለማገናኘት እንደሚሞክሩ   ባቀረቡት ሃሳብ መሰረት ... ሐስንም ሆነ ከዲር እንዲሁም ሁሴን ዳዲ፤ በከር ጂሎና ሐጂ ተመካክረው ተስማሙ። መጀምሪያ ግን  ከከዲር ዋቆ ወደ ሰላም እንዲገባ  እንፈልጋለን። እኛም ሁኔታውን እያየን ተራ በተራ ወደ ሰላማዊ ኑሮአቸው ለመመለስ ማለትም እጅ ለመስጠት ፍላጎት አለን።   ካሳሁን ስምምነቱን ይዘው ከሃሰን ቱሬ ሰላይ ኡመር ሃስን ጋር ወደ ጎባ በማቅናት ከእርሳቸውም ሆነ ከሐሰን ቱሬ ወዳጅ ከሆኑት አቶ ንጉሴ ገረመድሕን ቤት በሁለተኛው ቅዳሜ እቴቱ ላይ ደርሰው አዳር ያደርጋሉ። እቴቱ ከጎባ 10 ኪሎ ሜትር የምትርቅ የገጠር ቀበሌ ናት። በማግስቱም ኡመርን ንጉሴ ቤት ትተው እነ ከተማ ከእንቅልፋቸው ገና ሳይነሱ፤   ልጆች! ከተማ! አቡ! በሩን ክፍተሉኝ ሲሉ ተጣሩ። አሳዬ ጃጋማን በአስቸኳይ ለማነጋገር ቀርቶ ስልጣናቸውም በቀጠሮ እንኳን ቢሆን ለማነጋገር ስለማያስችሏቸው ዘዴ መፈለግ ነበረባቸው። ጊንር ሰራተኛ በነበሩበት ጊዜ በጣም ወዳጃቸው ና ጃጋማን በቀላሉ ለማግኘት የሚችል በቀለ ቱሉን ማነጋገር ነበረባቸው። እንዳሰቡትም በቀለ በሌላ ሁነኛ ሰው በኩል መልእክቱን ለጃጋማ እንዲድደርስ አንደረጉ። ጃጋማም በመገረም አቶ ከበደን ሰኞ ጥዋት በ 2.00 ቢሮአቸው እንዲመጡ አስጠሩዋቸው። ማ ታውኑ ከበደ የሆነውን ለካሳሁን ሲነግራቸው በጣም ተደስተው ጃጋማ ከተመቻቸው ንፍስ ለመቀበል ብለው በመኪና እቴቱ ድረስ ላይን ያዝ ሲል ቢመጡ ኡመርን...

መለስ ብዬ ሳየው 3

አቶ አድነው ስለ ኸረና ዘመቻ የሚያወጉት ሞልቶአቸዋል። “ሽፍቶች ሸሽተው ወደ ኸረና ደን ውስጥ ስለገቡ የረባ ጦርነት አልገጠመንም። ይሁን እንጂ፤ ነጭ ለባሽ መዝናናት አብዝቶ ነበር። አንድ ቀን ፍታውራሪን አጅበን ለአሰሳ ፈት ፊት ሲሄድ ዛፍ ሲወዛወዝ አየሁ። ዝንጀሮ ነው! ጉሬዛ ነው! ቢሉኝም አላመንኩም። ፍታውራሪም ተው ዝንጀሮ ነው አሉኝ። የለም እምቢ ብዬ ተኩስ ከፈትኩ!” “ወዲያው ከሽፍቶች አንዴ እሩምታ! ታ!ታ! ድም! ድም! ድብልቅልቅ ያለ ውግያ ሆነ። አድፍጠው ሊጨርሱን ነበር!ተከታተልናቸው!የታባታቸው! አመለጡን”!   ፍታውራሪም በዚህ ተደስተው ነፍሴን ያተርፍካት አንተ ነህ እያሉ ስለሚያሞግሳቸው አቶ አድነው በንቁነታቸው ይኩራራሉ። አድነው የማር ነጋዴነታቸውን ትተው በሀረና ዘመቻ ባሳዩት ወታደራዊ ንቃት የወህኒ ቤት ዘበኛነት ተቀጥረው ደሞዝተኛ ሆኑ። የንጉሱ ጉብኝትና የሰላም ጥሪ ዋናው ሽፍታ ዋቆ ጉቱ እጃቸውን ቢሰጡምና የባሌም ሽፍትነት በመንግስት ጦር ቢፈታም፤ ኸረና የመሽጉት የዋጎ ጉቱ ቀኝ እጆች፤እነ ሐሰን ቱሬና ከዲር ዋቆና ሁሴን ዳዲና የመሣሰሉት አሁንም እጅ አልሰጡም። ኸረና ከጎባ በስተደቡብ የሚገኝ ጥቅጥቅ ያለ ደን ነው። በመሆኑም እዚያ ውስጥ ወታደርም ሆነ ነጭ ለባሽ መላክ ሰው ማስጨረስ ካልሆነ ትርፍ ስለሌለው የቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ አገዛዝ ችግሩን በሰላም ለመፍታት ወይም አካባቢውን በአውሮፕላን ለመደብደብ ወስኗል። ገብሬ ሞረዱ ጡ!ጡጡ!ጡጡጡ!ጡጡ!ጡጡጡ “ንጉስ ነገስትህ!ንጉስ ነገስትህ! ኃይለ ስላሴ!ኃይለ ስላሴ! ሊ ጎ በ ኙ ህ! ሊ ጎ በ ኙ ህ! ይመጣሉና!ይመጣሉና! ጡ!ጡጡ!ጡጡጡ!ጡጡ! ቀዬህን አፅዳ! አጥርህን እጠር!   በርህንም ቀለም ቀባ! ብለውሃል! ጡ...

መለስ ብዬ ሳየው…2

መለስ ብዬ ሳየው….. ከቦጋለ   ካሣዬ ነጭ ለባሽ ሽፍታን ለመውጋት ዘምቷል። አዝማቹ ጣሊያንን በአርበኝነት ያርበደበዱት ጀግናው ፍታውራሪ ተገኔ ተሰማ ናቸው። ወንድማቸው ካፒቴን አጥሬ ተሰማ፤ ኢጣሊያ ተሸንፎ በማፈግፈግ ላይ እያለ አሳደው ከሰብስቤ ዋሻ ላይ በመማረክ እንደከብት አርደው ደሙን መጠጣታቸውን ድፍን ባሌ ያውቃል። የነ ከተማም አህያና ቆፍጣናው አጎቱ ዘምተዋል። የአጎቱ ሚስት ዘነበች ጉርሙ መሬት ይቅለላትና በሳንባ ነቀርሳ በልጅነቱ የተቀጨውን ብዙየን፤ ባሉዋ በዘመተ በሶስተኛው ቀን ወልዳ አራስ ናት።   ለአራስ ጠያቂ ተገንፍቶ የሚተረርፈውን ገንፎ ከተማና የአጎቱ ልጅ ጉቱ እየበሉ፤   አፋችሁን ተግሞጥመጡ! ምች እንዳይመታችሁ! የሚሉት ማስጥንቀቂያዎችም ሆነ ገንፎው ራሱ አንገሽግሾአቸዋል። የልጅ ነገር ሆዴን አመመኝ እንጂ መቼ በቃኝ ያቃል? ከበሉ በሁውላ ሮጠው ለመጫወት የሚሄዱት የሰፈሩ ልጅ ሁሉ የሚሰበሰብባት ሆን ተብሎ ለእግር ካስ ሜዳ የተሰራች የምትመስለው ሜዳ ላይ ነው። የከተማና የጉቱ አያት ሜዳዋ ሳር ስለምታበቅል ሳሩን አጭደው ከከመሩ በኋላ ዝናብ እስኪዘንብ ድርስ የሰፈሩ ልጆች ሜዳዋ ላይ ኳስ ቢጫወቱባትም ሆነ የሩጫ   ወድድር ቢያደርጉባት አይቆጡም። ሌላ ጊዜ ግን ውርድ ከራሴ ነው! ድርሽ ማለት የለም። የተያዘ በሳማ ነው የሚለበለበው። ነጭ ለባሽ ውጊያውን እያፋፈመው ነው። የእሳቱ ነበልባል ፋሲል ተራራን ከሩቁ ወለል አድርጎ ያሳያል። ከሜዳዋ ላይ የቃጠሎውን ትእይንት ለማየት የሰፈሩ ልጆች ተሰብሰበው፤ ኸረ ጎበዝ! እህም ነው!! ሽፍታ ጠግቧል እህም ነው!! እንበለው!! ልጆች እንደዛ ሲፈነጥዙ እናቶቻችው፤"ኸረ እናንተ ልጆች ወደ ቤት ግቡ!" "ወየውላቸው ዛሬ!" በማለት...

መለስ ብዬ ሳየው... (ቦጋለ ካሣዬ)

..."ጥሩ ገንዘብ እዛ የተማሪ እግር ኩዋስ ሜዳ ውስጥ ገብታለች! ሂድና ቶሎ ይዘሃት ና!" ወረፍ ሳይበዛ እንሄድ!" የአቡ እናት የተለመደ ትእዛዝ ነው። የጥሩ ገንዝብ እናት ከአህይት ሌላ የተለየ ስም ሳይወጣላት ጅብ በላት። ጥሩ ገንዘብ... ገና አሃዱ ተብሎ ከጀርባዋ ላይ ጭነት ያረፋባት ቀን እንደሌሎች ልትለግም ይቅርና ... አልፋ ተርፋ... የአህዮች ፊት መሪ በመሆኑዋ ነው ጥሩ ገንዝብን የመሰለ ስም ከአቶ አሳዬ የተቻረቺው። ወረፋው ደግሞ የወፍጮ ቤቱ ነው። ጋሽ መሃመዶ ይባል ነበር ተቆጣጣሪው። በጣም ደግ ሰው ነበር። መቼም በህይወት ሊኖር አይችልም.... እድሜ እንደ ማቱ ሳላ ተለግሶት ካልሆነ። .."አንተ አቡ ቆይ! ቆይ! የጋሼ አሳዬ ልጅ አይደለህ? አዎ! አህያዋን(ጥሩ ገንዘብን) ነጭ ለባሾች ስንቃቸውን ጭነውባት ሄደዋል በለው! አይዚህ አይቆጣኽም! ነጭ ለባሽ የአገር ፀጥታ ሲደፈረስ ከመደበኛ ሰራዊት ውጭ ሰላም እንዲይስከብር የሚጠራ ዘማች ነው። ነፍጠኛ የሚሉት ነው። አማሮች ብቻ አይደሉም ታዲያ። ሰላሌዎችና ጉራጌዎች አሉበት። ባሌ ጎባ ድሮ ጠሃይ ከጠለቀ በሁውላ ድቅድቅ ባለ ጨለማ ነው የምትዋጠው። ሰማዩ ካልዳመነ ግን ከዋክቦቶችዋ የሚሰጡት ብርሃንና በተለይ ተወራርዋሪዎቹ የሚሰሩት ትእይንት ታይቶ የሚጠገብ አይደለም። ወቼ ጉድ ...አንድ አውራጃ ሙሉ አገር ከዋክብት ለማየት እንድንችል የመንገድ ዳር መብራት እንዳይተከልበት! ብለው አሻፈረኝ ያሉት የፍሪዢያን ፈርንጆች... ደሜን ከደማቸው በመቀላቀሌ ይሆን? ስለ ከዋክብት ሳነሳ ትዝ አሉኝ። ከዋክብትን ማየት ማራኪ ነው። ጎባ የእዛን እለት ግን ዝናብና ደመና ነው። ይህም ሆኖ ድሮ ከጎባ በስተደቡቡ በጭራሽ በጨለማ የማይታየው የፋሲል ተራራ በአካ...