Posts

Showing posts from August, 2014

ግንባር? ውህደት? እየተስተዋለ!

       ግንባር? ውህደት? እየተስተዋለ!                 ‘ነጻነቴን ከኢሳያስ መንጋጋ አገኘዋለሁ ማለትህን ተወኝ!’                         ቦጋለ ካሣዬ (አምስተርዳም ኦገስት) በኢሳያስ አፈወርቂ ‘እየተደገፉ’፤ ወያኔን ከስልጣን ለማስወገድ የትጥቅ ትግል እናካሄዳለን የሚሉ ሶስት ድርጅቶች አንድ ግንባር ለመፍጠርና ወደፊትም ለመዋሃድ መስማማታቸውን በቅርቡ የግንቦት-7ቱ ኢሳት በሰበር ዜናው ነግሮናል። የዲያስጶራውም ሰሞነኛ መነጋገሪያ ነጥብ ሁኖአል። ከዜናው ትንሽ ቀደም ብሎ የኢሳቱ ዋና ሰው ፋሲል የኔአለም፤ የወያኔ መውደቂያው ዶርሶአል ሲል ተቁነጥንጦ በፊስቡኩ ላይ የለጠፈው የመልካም ምኞት ብስራት፤ ፍጥምጥሙ ያለቀ ጉዳይ መሆኑን ያመላክታል። ዜናው ወያኔ በማንኛቸውም መንገድ ተወግዶ ለማየት ለሚሹ ገራገር ኢትዮጵያውያን ክፋት ያለው አይደለም። ሌላም ሰው ቢሆን ጭቆና ባለበት የትጥቅ ትግልን ማስቆም እንደማይቻል ስለሚገነዘብ፤ ተዋጊዎቹ ግንባር መፍጠራቸውን ክፉ ነገር ነው! ብሎ ቢያንባርቅ የፖለቲካ ሀሁ ያልገባው ቂላቂል ተብሎ ሊቆጠር እንደሚችል አይስተውም። ለነገሩ ጠላት አይናቅምና፤ ግንባሩን እንደ ክፉ ነገር ሊያይ የሚገባው ወያኔ ይሆን እንዴ? ‘ናይ ፖለቲካ ናጽነት አይኮነን ሆድ ናጽነት !’ በቅርቡ ወያኔ መጪውን ምርጫ ተከትሎ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ...

እኛ ተማሪ እያለን.... ሕንድ በዛ!

                    እኛ ተማሪዎች እያለን፤ ሕንድ በዛ ! እ . ኢ . አ በ 1964 ነው። ባሌ ጎባ ነው አገሩ። ትምህርት ቤቱም አዝማች ደግለሃን ይባል ነበር። ከ 7 ኛ እሰከ 12 ኛ ክፍል የሚከታተሉ ተማሪዎችን የሚያስተናግደበት፤ ከድንጋይና ከእንጨት የተሰሩ ክፍሎችም ነበሩት። ተራራ ብቻውን ታሪክ የሚሰራ ይመስል፤ ታሪካዊ ስሙ በደንቆሮው ደርግ ጊዜ ተፍቆ ባቱ ተራራ ተብሎአል። ታዲያ በዳግልሃን ት / ቤት ውስጥ ሕንዶች በዙ ! ተባለ። አሁን ልብ ብዬ ሳየው፤ ‘ ሕንዶች ’ እንላቸው የነበረው፤ ፊሊፒኖችንም ጭምር ነው። አንድ ሕንድ ወይም ፊሊፒኖ አስተማሪ በአንዴ ሂሳብ፣ጆግራፊ ወይም ታሪክ እንዲያስተምር ይመደባል። እንግሊዠኛና ሂሳብ የሚያስተምሩም ነበሩ። አንዳንዶቹ አስተማሪዎች በቂ ዝግጅት ስላልነበራቸው ሽምድደው የመጡት ነገር ጥያቄና መልስ ከጎበዝ ተማሪዎች ሲያስነሳ ብስጭት ውስጥ ይገባሉ። ወይም በነገ ይደር እየተባለ ጥያቄዎች ሳይመለሱ እንዲረሳሳ ያደርጋሉ። እኛ ገና የሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ነበርን። ከኢትዮጵያውያን በስተቀር አንድም የውጭ አገር ዜጋ እኛን እንዲያስተምር አልተመደበም። ታዲያ ከላይ የሆነውን ያወጋዋችሁ፤ ሕንዶች በዙ ! ጥሩ አስተማሪዎች ስላይደሉ፤ እነርሱ ሊያስተምሩን አይገባም። ሌላ ጥሩ አስተማሪዎች ይመደቡልን፤ እያሉ የዳግለሃን የተማሪዎች ካውንስል ከተማሪዎች ጋር ...