Posts

Showing posts from May, 2025

ትንሹ እስክንድር ነጋ!

Image
                         ትንሹ እስክንድር ነጋ፤ ጋዜጠኛና አርበኛ ጌጥዬ  ያለው ባለፈው ስለ አንዳንድ አሞላቃቂ ጥቅመኞች የኢሳት ፍርስራሽ ሚዲያዎች የከሰረ የጋዜጠኝነት ስነምግባር ይዘቶች በደምሳሳው አይተናል። ዛሬ አንድ ሌላ ማንሳት በሚገባን፤የኢትዮ-360ው፤ አይጠገቤ ጋዜጠኛና አርበኛ ጌጥዬ ያለው እንጀምር። ጌጥዬ በሞራል ከፍታው ትንሹ እስክንድር ነጋ ሊባል የሚገባው ነው።ከትግል ሜዳ ሆኖ ከየፋኖ ውሎ ፕሮግራሙ በተጨማሪ፤ የሚሰጣቸው ትንታኔዎች ሰፊና ጥልቅ ንባቡን የሚያንፀባርቁ ናቸው። የማያውቀውንም አላውቅም ነው የሚለው። ትሁትና የሰላ አእምሮ ነው ያለው። ሲወድም ሲተችም አያዳላም። እውነተኛ ሰው ነው። የጌጥዬ የድምፅ ፍሰትና ቃና አድማጭን ከመቀመጫው እንዳይነቃነቅ የሚያደርጉ ማግኔቶች ናቸው።ሌሎች ከጊጥዬ መማር አለባቸው።በሚዲያ ላይ ቀርቦ መቆጣትና መደንፋት የአድማጭን የማድመጥ አትኮሮት ይቀንሳሉና።በዚህም መሰረት ኢትዮ-360 ለእውነት በቆሙ የአማራ ይሁን የኢትዮጵያ ልጆች የተካተቱበት ስለሆነ በገንዘብም በሃስብም ሊደገፍ የሚገባው ተቁዋም ነው። ከኢሳት ፍርስራሾች ውጭ ብዙ ሚድያዎች አሉ።የጣና ቲቪ እስካሁን ለፋኖ ትግል እየሰጠ ያለው አበርክቶ ግሩም ነው። ከኢትዮ-360 ጋር ስራቸውን በቅንጅት ሊሰሩ ቢችሉ ጥሩ ይመስለኛል፤ ችግር ከሌለ።አብረው ለፍኖ መሪዎች ጥሪ በማድረግ የአመራር ብቃታቸውን ህዝብ የሚመዝንበትን መድረክ ማመቻቸት ይችላሉ። ጥሪ አድርገው እምቢ የሚሉትን ለህዝብ ማሳወቅ ይገባቸዋል። ይኼን ማድረግ ጥቅሙ ብዙ ነው። እንደው በጥቂቱ፤ መጀመሪያ የፋኖ ግለሰብ ታጋይ እውነተኛ መሪዎቹን በትክክል እንዲያውቅ ያ...

አሞላቃቂ ጥቅመኛ!

ስልጡን ይሁን ገልቱ አመራር በስልጣን ላይ የማስቀመጥ ሃላፊነት የሕዝብ ነው፡፡ሕዝብ ደግሞ ሃላፊነቱን በቅጡ ለመወጣት እውነተኛ መረጃ ያስፈልገዋል። በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙሃን ካለመታከት መልካም ስነምግባርን በማበረታታት፤ ለሕብረተሰብ የማይጠቅምን ድርጊት ይሁን ሃሳብ ጠንቅነቱን በማስተማር፤ ለህዝብ ቆመናል በማለት የሚሞላቀቁትንና ሃቀኞቹን የስልጣን ተፎካካሪዎች ተከታትለው ማንነታቸውን በማስተዋወቅ  ትልቅ አጋዥ ሚና ሊጫወቱ ይገባል፡፡ ፋኖና የኢትዮጵያ ዲያስጶራ ሚዲያዎች ፋኖ ባለፉት 2 አመታት የትጥቅ ትግል ከጀመረበት ጀምሮ በማህበራዊና በሳተላይት መረጃ የሚያስተላልፉትን ሚዲያዎች፤ የኢሳት ፍርስራሾችና ሌሎች ብለን ልንከፍላቸው እንችላለን፡፡ የኢሳት ፍርስራሾች ወያኔን ለመታገል በግንቦት 7 የተመሰረተው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን(ኢሳት) የዲያስጶራው ድጋፍ ነበረው፡፡ብዙዎቹ ጋዜጠኞቹም ወያኔ በቅንጅት መሸነፉን አልቀበልም ብሎ ባሳረፈባቸው ዱላ አገራቸውን ጥለው የተሰደዱ ናቸው። ኢሳት ወያኔን ታግሎአል። ይሁን እንጂ በግንቦት 7 ፖለቲከኞች ቁጥጥር ስር ስለነበረ ነጻ ሚድያ አልነበረም። ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ከሻእቢያ ጋር መስራት እንደጀመሩ፤ኢሳት ለብሄረተኞች ሰፊ መድረክ በመስጠት በቅንጅት መንፈስ ጠውልጎ የነበረውን ጎሰኝነት እንዲለመልም አፍራሽ ሚና ተጫወተ። የግንቦት-7ን የፈጠራ ወታደራዊ ኮሚንኬ በማስራጨት አማራው በተለይ በጎንደር በወያኔ እንዲመታ ዱላ አቀበለ። ኢሳት ሁነኛ ተቁዋም ሆኖ እንዲዘልቅ ከግንቦት 7 ይላቀቅ የሚለው ውትወታ በጊዜው ስሚም አላገኘም፡፡ የአገር ፍቅር እንጂ የፖለቲካ እውቀት የለኝም የሚለው የኢሳት የገንዘብ ዋና አሰባሳቢ አርቲስት ታማኝ በየነ፤ “ኢሳት የግንቦት 7 ቢሆንስ?” እያለ ይሳለቅ ነበር።...