Posts

Showing posts from April, 2024

እስክንድር ነጋና አማራ

እስክንድር ነጋና አማራ አንድ ለመንገድ /3/ …  ባለፈው አንድ ለመንገድ/2ኛ/ ዳሰሳ፤ \እስክንድረ ነጋና አማራ/ ከእስክንድር ስራ የተወሰደ መሆኑን ገልጫለሁ። አሁን ወደ መጨረሻው ሶስተኛው ክፍል ደርሰናል። ዳሰሳውን ዘርዘር አድርጌ ያቀረብኩትም እስክንድር እንዴት ስለአማራ ህዝብ እንደሚጨነቅ የጻፈውን ስራ ለማስተዋወቅ ነው። ያነሳሳኝ ጉዳይም   ባለፈው ወር በህብር ሬዴዮ አንድ የፋኖ ‘ቃለ አቀባይ ነኝ’ ባይ መስሪ ወይም ደንቆሮ ስለ እስክንድር የተናገረውን ፍሬፈርስኪ ካዳመጥኩ በሁዋላ ይኼ የእስክንድርና የፕሮፌሰር መስፍን ሙግት ‘ለቃለ አቀባዩም’ ለተቀረው አንባቢ ግንዛቤ ይሰጣል በማለት ነው። አንድ ለመንገድ /3/  እስክንድር ነጋና አማራ እስክንድር በኮሚኒስቶች መስፍርትም ቢኬድ አማራ ጎሳ/ብሄር/ማህበረሰብ ለመባል፤ከአምስቱ መስፍርቶች፤ የጋራ ቁዋንቁዋ፣ስነልቦና ታሪክና መሬትን ያሙዋላል ይላል። የማያሙዋለው የጋራ ኢኮኖሚ ነው። በኢንዱስትሪ የዳበረ ኢኮኖሚ እንኩዋን አማራ ኢትዮጵያም ስለሌላት፤ ነገድ ለመባል የኢኮኖሚውን መስፍርት ማሙዋላት አይጠበቅበትም።ኮሚንስቶችም ሁሉም መስፍርቶች መሙዋላት አለባቸው አይሉም። ይሁን እንጂ ከመስፍርቶቹ መቅረት የሌለበት የጋራ ስነልቦና ነውና በዚህ ረገድም የአማራ ነገዳዊ ማንነት አሌ የሚባል አይደለም። እስክንድር ገሪማ ታፈረ( የታዋቂዊው ፊልም ሰሪ ኃይሌ ገሪማ አባት) ስለ አማራ 25 ዓመታት ሙሉ ያጠኑትን አለቃ ታዬ የሚባሉትን ሊቅ በመጥቀስ እ.ኢ.አ 1973 የጻፉትንም ያጋራናል። ገሪማ አለቃ ታዬ አማራ የሚባለው ህዝብ ትውልዱ ከሴም ልጅ ከኤቦር ነገደ ዮቅጣን መሆኑን አረጋግጠዋል ይላሉ።ጥናታቸውም የተመረኮዘው፤ በአለም ታሪክ ተመራማሪዎች ስራ(ኢዘንበር፣መልዚ፣ፓስቴንና ቫንሲን)፣ከመልኩ(...

መነሻችን አማራ መዳረሺያችን ኢትዮጵያ!

  መነሻችን አማራ መዳረሺያችን ኢትዮጵያ!   አንድ ለመንገድ /2/ ... እስክንድር ነጋና አማራ ቀጥለን እስክንድር በ1996(የዛሬ 20 አመት) በጋዜጠኛነቱ “አማራ የለም” ብለው ከሞገቱት ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ጋር ያደረገውን ክርክር በደምሳሳው እንመለከታለን፡፡ እግረመንግዳችንንም ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፤ “አንዳንድ ምሁራን አማራ የለም ሲሉ ይደመጣሉ፤ የአማራ ጠላቶች ግን አማራውን ለይተው ለማጥቃት ሲቸገሩ አናይም” ብለው አማራ የለም ባዮችን መተቸታቸውን ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ አስራት “ ለአማራ ጦርነት ማስተማር፤ እናት ለልጁዋ ምጥ እንደማስተማረች ይቆጠራል ” ብለው አማራ እንዲዋጋ በጥዋቱ አስጠንቅቀውት ነበር፡፡ዘግይቶም ቢሆን ዛሬ እውነቱን እያየነው አይደለም እንዴ? አማራ እስክንድር ፕሮፈሰር መስፍን አማራ የሚባል ጎሳ የለም፤ [1] ቃሉ ለክርስትና ነው የሚቀርበው ያሉበትን በቂ መረጃ አላቀረቡም ይላል፡፡ ፕሮፌሰሩ እንደ ምንጭ የተጠቀሙባቸው ከሳቴ ብርሃን ተሰማ፣አለቃ ደስታ ተክለወልድ፣ አለቃ አ ጽ ሜና በአባ ዪሃንስ ገ/እግዚአብሄር (ትግርኛ) መዝገበ ቃላት የሰፈሩት ፍቺዎች አንድም ቦታ አማራ ክርስቲያን ማለት ነው የሚል የለባቸውም፡፡ ፕሮፌሰር ያጣቀሱት የአለቃ ደስታ ተክለወልድ፤አማራ ማለት ተጠምቆ ተገዝሮ፤ ማተብ አስሮ ቢልም አማራ የሃይማኖት መጠሪያ ነው አይልም፡፡የአለቃው ማብራሪያ የሳውዲ ዜጋ ለመሆን እስልምና መቀበል ወይም የእስራኤል ዜጋ ለመሆን(ከጥቂት አረቦች በስተቀር) የአይሁዲ ሃይማኖት ተከታይ መሆን እደሚያስፈልግ አይነት ተመሳሳይነት ያለው ነው፡፡ ዐማራ ለመሆን ለምን ክርስቲያ መሆን አሰፈለገ? ሲል እስክንድር ይጠይቃል፡፡ነገሩ ከታሪክ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ እንደ እስክንድር ከሆነ ምክንያቱ ሙስሊ...