Posts

Showing posts from March, 2014

ወርቅ-ቅብ፣መርዘኛ ብእር። እኛም አውቀናል፤ ጉድጉዋድ ምሰናል!

ወርቅ-ቅብ፣መርዘኛ ብእር። እኛም አውቀናል፤ ጉድጉዋድ ምሰናል! ከቦጋለ ካሳዬ፤ ማርች 2014 አምስተርዳም የአፈንዲ ሙተኪ ጮሌነት ፀሃይ ሞቆታል። በዚህም ምክንያት ተጨንቆ በትክክል ማሰብ እንደተሳነው ከመጣጥፎቹ መረዳት አዳጋች አይደለም። አፈንዲ የከሸፈውን የተስፋዬ ገ/አብን ተልእኮ፤ ከውስጣችን ተቀላቅሎ ረቀቅ ባለ መንገድ እያካሄደ የሚገኝ ለምድ የለበሰ የቀበሮ ባሕታዊ ነው። ብዙ ክሶችን ደረደርኩ አይደል? ምክንያቶቹን እንያቸዋ አብረን።   1.በኦነግነት ተከሰስኩ ብሎ በሰጠው ምላሽ ላይ፤ ኦነግን ይደግፍ እንደነበርና፤ አሁን ግን በኦነግ የመገንጠል አቁዋም ላይ ስለማይስማማ እንደማይደግፈው ነግሮናል። ሃቀኝነት ያለው ምላሽ አይደለም። 1.1 በዚሁ ምላሹ፤ በቂ ዋቢ ሳይጠቅስ ‘ኦነግ አደረጋቸው’ ተብሎ ሲጻፍና ሲነገር የነበረውን ወንጅሎች፤ በአንድ ቦታ  ከተፈጸመው ወንጀል በስተቀር ውድቅ አድርጎለታል። እውነት ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ ከእርሱ ገና ድሮ ቀድሞ ኦነግ ከሽግግሩ መንግስት ከመውጣቱ በፊት እርሱ በሚያስተዳድርበት አካባቢ ስለተፈጸመው ወንጀል ሃላፊነቱን እንደሚወስድ ራሱ ስለነገረን፤ የአፈንዲ ማብራሪያ መረጃ ላልነበራቸው ሰዎች ይጠቅም ካልሆነ በስተቀር፤ ለብዙዎቻችን ተደጋጋሚ ነገር በመሆኑ ምንም ተጨማሪ ፋይዳ አላየንበትም። በነገራችን ላይ እኛ እራሳችንን “እኛ” የምንለው፤ እኔ የሚለው ተውላጠስም ስለ ራስ የገነነ እድምታ እንዳይፈጥር በመስጋት ነው። እኛ የምንጽፋውም ሃሳብ ቀደም ሲል ሌሎች ያጤኑት ወደፊትም ሊሎች ሊያጤኑት እንደማይቀሩ ከግንዛቤ በማስገባትም ነው። ቀዳማዊ ኃይሥላሴ ግን “እኛ”ይሉ የነበረው፤ የዘውዱ፣የሃይማኖትና የሕዝቡ ተቀቢ፣ተወካይና ገዢ መሆናቸውን ለማንጸባርቅ እንጂ፤ አፈንዲ እንዳለው የሐረር ሰው ስ...

" ሃረጉ ይሙት ጋ. እም. ይወዳል"

“ሃረጉ ይሙት! ጋ. እም. ይወዳል!” ቦጋለ ካሣዬ  ማርች 2014 አምስተርዳም መግቢያ፤ የፌስቡኩ(Facebook) ኤትኖግራፈር፤የኤርትራው ኢሳያስ አፈወርቂ አንዳንድ አሁን በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ካሉት ኢትዮጵያውያን የተሻላ ለኢትዮጵያ ያስባል ብሎ በመጻፉ የተነሳ፤ ለተስነዘረበት ምላሽ፤‘ተስደብኩ’ እያለ  በሞራል ጥያቄ ስርቻ ውስጥ ለመወተፍ መውተርተሩን አጤነናል። ከንቱ ልፍት። ነገሩ ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል አይነት ነው። እንደ ኢማኑኤል ዋለርስታይን ከሆነ፤ በምእራቡ ዩኒቨርስቲዎች ማሕበራዊ ሳይንስ፤  በታሪክ፣በኢኮኖሚክስ፣በሶሶሎጂንና በፖለቲካ ሳይንስ ላይ ብቻ ላይ ነበር ተከፋፍሎ የሚጠናው። ይሁን እንጂ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሃያል አገሮች በተቀረው ዓለም ላይ ቀንበራቸውን ሲጠምዱ፤ እነርሱ ሁዋላቀር አርገው የሚቆጥሩትን ሕዝቦች ለማጥናት ማህበራዊ ሳይንስንም ማስፋት አስፈለጋቸው። በዚህም መሰረት አንትሮፖሎጂን በዩኒቨርስቲዎች ማስተማር ተጀመረ። አንዱ የአንትሮፖሊጂስቶች ስራ በሕዝቡ መሃል እየኖሩ፤ ቁዋንቁውን በመናገርም ይሁን በቱርጁማን ፣ባሕሉንና አኑዋኑዋሩን አጥንተው ለቅኝ ግዛት አስተዳዳሪዎች ስራቸውን ማቅረብ ነበር። በሚገኘው መረጃም ቅኝ ገዚዎች ሕዝቡን እንዴት ማስተዳደር እንደሚገባቸው ይገለገሉበት ነበር። ሕዝቡን የሚያጠኑበት ዘዴ፤ በማየትና በመሳተፍ የሚደረግ ስለነበር፤ ስራቸው “ኢትኖግራፊ መጻፍ” ይባል ነበር። እንግዲህ ኢትኖግራፊ የቅኝ ግዛት ‘ቱሴ’ ወይም መረጃ አቀባይ ነበርም ማለት ነው። ወደ ቡዳ ኢትኖግራፈሮች እንሂድ። 1ኛ/፤ አንደኛው ቡዳ  ለሻእቢያ ያረገደው  አስመሮም  ነው። እርሱ በጻፈው የኦሮሞ የገዳ ስርዓት ስራ ላይ ተመርክዞ ነው፤ የሻእቢያው ስላይ ተስፋዬ ገብረአብ ፤ ...