Posts

Showing posts from 2013

በበርበሬ! ከቦጋለ ካሣዬ(አምስተርዳም)

ከቦጋለ ካሣዬ ( አምስተርዳም ) የመጀመሪያው የባሌ ጎባ አዝማች ደግለሃን ትምህርት ቤት ግድግዳውና ወለሉ በእንጨት ነው የተሰራው። ታዲያ የጎባ የእድገት በሕብረት አዝማች ሆኖ የተላከውን መኮንን፤ መሬት ይቅለላቸውና እነ ታምራት ያለው እጁን የፍጥኝ፤ እግሩንም አስረው በርበሬ አጠገቡ በመነስነስ፤ « ለወታደር መንግስት፤ ሕዝብ ላልወከለ ! አልገዛም አለ፤ ሕዝቡ እየታገለ ! አንገዛም ! አንገዛም ! አንገዛም !!» እያሉ በመዘመር የጣውላውን ወለል ሲረግጡት በርበሬው እየቦነነ ሰውየው አይኑ ውስጥ ይገባል። የሰውየው አይን ተጎልግሎ ሊወጣ ያለ እንደነበር እስከዛሬ ይታየኛል። እኔና አብሮ አደጌ አብርሃም ያኔ ዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች ስለነበርን አልዘመትንም። ታዲያ ዘማቾች ቅጥር ግብያችን ውስጥ ለስብሰባ መጥተው ነው፤ ወታደር አዝማቻቸውን በበርበሬ ሲለበልቡት የምንታዘበው። መዝሙሩን ግን ወደነዋል። አሁን ዝም ብዬ ሳስበው አድራጎታቸው ሰላማዊ ባይሆንም፤ የወታደራዊውን አገዛዝ እንዴት ይጠየፉ እንደነበርና ለራሳቸው ደሕንነት ምንም የማይፈሩ ወኔ ያላቸው ትኩስ ወተት የጠገቡ አንበሶች ሆነው ይታዩኛል። ታምራት ያለው ሲዘምት የ 11 ኛ ክፍል ተማሪ ነበር። ጋሼ ወልደሰማያት የሚባል የሂሳብ አስተማሪ ነበረን። ሰነፍ ስለነበር ብዙውን ግዜ ቀላል ቀላሉን ነገር ነው የሚስተምረን። አንዳንዴ ታምራት መጥቶ እንዲያስተምረንም ያደርግ ነበር። ታምራት ከጋሽ ወልደሰማያት አስር እጥፍ ይበልጣል ! ታዲያ ያልገባንና ጋሼ ወልደሰማያት የሚያልፈው...

6 አስተያየቶች፤ በዴሞክራሲና ሁለንተናዊ ልማት በኢትዮጵያ...

መጽሐፍ፤ ዴሞክራሲና ሁለንተናዊ ልማት በኢትዮጵያ፤ በብርሃኑ ነጋ 6 አስተያየቶች፤   ከቦጋለ ካሣዬ አምስተርዳም ስለ መጽሐፉ፤ በምረቃው እለትም ሆነ ከዚያም በሁዋላ የተሰነዘሩትን አስተያየቶች አዳመጥኩ። አነበብኩ። አንብቤው ከጨረስኩ በሁዋላ ግን አብዛኞቹ አስተያየቶች ሙገሳ ብቻ ሆነው ነው የታዩኝ። የግል ( ተዛማች ) ትችቴንና አስተያየቴን በስድስት ነጥቦች ላይ አቀርባለሁ። 1. መፈናቀል ደራሲው በመግቢያው ላይ ከልጁ ኖህ ጋር ስለ አደረገው የስራ ‘ ውልና ’ በገዛ ልጁ ችሎታ መኩራቱን በመጻፉ የብዙዎቻችንን ስሜት ነክቶታል። ኖህ እጅግ ደስ የሚል ፍሬ ነው። ቅር የሚለው ነገር ግን የአሜሪካ ሲሳይ መሆኑ ነው። ሌላም የሚስያተክዝ ነገር በአእምሮ ይመጣል። አባባ ነጋ በአገራቸው ውጣ ውረዱን ተቁዋቁመው የተዋጣላቸው ከበርቴ ሆኑ። ራሳቸውንም ሆነ አገራቸውን ጠቀሙ። ልጃቸው ብርሃኑ ግን ገና በ 17 አመቱ የፖለቲካ ጉጉት አደረበት። ከዚያም ‘ በአህያ አስተሳሰብ ’ የሚል ስድብ መዘዝ ከተቃጣ ዱላ ’ ነፍስ አውጭኝ ተርፎ፤ አሲንባ ሸፈተና በሱዳን በኩል አሜሪካ ተሰዶ እዚያው ተማረ። በፖለቲካ ጉጉት ምክንያት ወደ አገሩ ተመለሰ። ከዚያስ ? ከንቲባ፣ ቀጥሎም ጠቅላይ ሚንስትር ሊሆን ይችል ነበር። ወይኔ ! ወንድሜን ! ስልጣን ለትንሽ አመለጠቺውና እንደገና አገሩ መኖር አልተመቸውም። አሁን ወደ አሜሪካ ተመልሶ አሜሪካኖችን ያስተምራል። ዛሬም ለአርባ አመታት የቀጠለው የፖለቲካ ጉጉቱ አለመርካቱ ብቻ ሳይሆን፤ አቅጣጫውም አነጋጋ...