Posts

Showing posts from October, 2024

እስከ ስባት ትውልድ!

ልደቱ አያሌው... እስከ ሰባት ትውልድ!                               ቦጋለ ካሣዬ የፖለቲካ ውይይቶች በፖሊሲ ላይ የተመሰረቱ መሆን ቢኖርባቸውም እንደየአገሩ ልሂቃን የፖለቲካ ባህል ይዘታቸውና ቃናቸው ይለያያሉ፡፡ ኢታሊያዊው ፋውስቶ በርቲኖቲ እንደ ልደቱ አያሌው የመናገር ችሎታ ካላቸው ፖለቲከኞች አንዱ ነው፡፡ማህበራዊ ፍትህ ለኢታሊያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለአለም ህዝብ ሁሉ የሚመኝ ሃቀኛ ሰው ነው፡፡ መሃንዲስ ነው።በሰራተኛ ማህበራት ውስጥም መሪ ሆኖ ሰርቶአል፡፡በስሎ ነው ወደ ፖለቲካ አለም የገባው፡፡ተልእኮው የካቲታሊዝምን ያልተገራ የሃብት ቅንቅን ማጋለጥ እንጂ የካቢኔ ሹመት አይደለም፡፡ የሚናገረው ሁሉ እውነት ስለሆነ ማንም አጭበርባሪ ኢታሊያዊ ፖለቲከኛ ይሁን አድርባይ ምሁር ከእርሱ ጋር በአደባባይ ለመወያየት አይደፍርም፡፡ራእይና እውነት ያለው ሰው ነው፡፡ “la Citta’ degli uomini”/2007 ( የወንዶች ከተማ) የሚል መጽሃፉ ተደጋግሞ ቢነበብ አይሰለችም። የአብይ አህመድ የመደመር ዝባዝንኬን ግን ገልጦ 30 ገጽ መድረስ ትልቅ አቀበት ነው። ሌላ የማውቀው የልደቱ ተመሳሳይ የንግግር ችሎታ ያለው ሰው የዳቹ ያን ማርያኒሰን ነው፡፡ እርሱም የማህበራዊ ፍትህ ጠበቃ ነው፡፡ የሰሜን አትላንቲክ ትብብርን አጥብቆ የሚያወግዝና እንዲሁ እንደ በርቲኖቲ የካፒታሊዝም ቅንቅን የሚራገፍበት አለም ማየት ነው ምኞቱ፡፡ ያን ራሱን በንባብና በልምድ ያዳበረ ሰው ነው፡፡ ውሸት አይወድም፡፡ ልደቱ አያሌው ልደቱ አያሌው በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የተከሰተው በጉርምስና እድሜው ከመኪና ንግድ ውጭ ምንም የስራም ሆነ የትምህርት ...