Posts

Showing posts from June, 2024

ዴሞክራሲ ስር በሰደደበት አገሮች ....

    የካናዳ የሰብዓዊ መብቶች ንዑስ   የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ፤ የ ኢትዮጵያን ጉዳይ በሚመለከት ያዘጋጀውን ወቅታዊ ግምገማ  አስመልክቶ የተሰጠ አስተያየት። ቦጋለ ካሣዬ/አትዋ ዴ ሞክራሲ ስር በሰደደበት አገሮች የህዝብ ተወካዮች ስልጣን ላይ ያለውን አካል ስራውን በትክክል መስራቱን በጥንቃቄ መገመገም ትልቁ ሃላፊነታቸው ነው። በዚህም መሰረት መረጃዎችን አሰባስበው አገራቸውን ሊጠቅም ይችላል ብለው የሚያምኑበትን የፓሊሲ ሃሳብ ያቀርባሉ።   በዚህም ምክንያት የካናዳ የሰብዓዊ መብቶች ንዑስ   የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያውያንን በማሳተፍ ስለ አገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ለማዳመጥ በጁን 11/2024 መድረክ ፈጥሮ ነበር። ስድስት ኢትዮጵያውያን ነበሩ እንዲገኙ የታሰበው። የአማራ ተወካይ አለመጋበዙ ስለታወቀ፤ በአማራ ማህበራት በተደረገው የቅሬታ ዘመቻ አማራ እንዲወከል ተደረገና ሰባት ኢትዮጵያውያን ተሳተፉ።   1.      ዶ/ር ዪናስ ብሩ ከአሜሪካ በቪዲዮ ተካፍለዋል። በአለም አቀፍ ተቁዋም ባለቸው ልምድ፣የአብይ አህመድ አማካሪ ስለነበሩና በቁዋንቁዋ ችሎታቸውም የህዝብ ተወካዮቹን ቀልብ ስለሳቡ ብዙ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው  የሚያምኑበትን ሃሳብ ለማራመድ የተሻለ እድልና ጊዜ አግኝተዋል።   ይሁን እንጂ ዶ/ሩ እንደተለመደው ስለባውንና ግፍ አይፈሬዎቹን አንድ ላይ እንደ ወዳጃቸው መራራ ጉዲና አጃምለው ሲከሱ ተደምጠዋል።  የዘር ፍጅት በአለም አቀፍ ገለልተኛ አካል እስካልተረጋጋጠ ድረስ በኢትዮጵያውያን አክቲቪስቶች የሚቀነቀነው ተቀባይነት የለውም በማለት፤ የብልጽግና፣የኦነግንና የወያኔን የ...